...

Amharic Quran

አስ ሷፋት

بسم الله الرحمن الرحيم

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

37:1

መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡

🔊 📋 🔍
37:2

መገሠጽንም በሚገሥጹት፤

🔊 📋 🔍
37:3

ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡

🔊 📋 🔍
37:4

አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:5

የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:6

እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡

🔊 📋 🔍
37:7

አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡

🔊 📋 🔍
37:8

ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡

🔊 📋 🔍
37:9

የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:10

ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡

🔊 📋 🔍
37:11

ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:12

ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡

🔊 📋 🔍
37:13

በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡

🔊 📋 🔍
37:14

ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:15

ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡

🔊 📋 🔍
37:16

«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?

🔊 📋 🔍
37:17

«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
37:18

«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:19

እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:20

«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡

🔊 📋 🔍
37:21

«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
37:22

(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡

🔊 📋 🔍
37:23

«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:24

«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡

🔊 📋 🔍
37:25

(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
37:26

በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:27

የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:28

(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:29

(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡

🔊 📋 🔍
37:30

«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡

🔊 📋 🔍
37:31

«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡

🔊 📋 🔍
37:32

«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
37:33

ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:34

እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

🔊 📋 🔍
37:35

እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡

🔊 📋 🔍
37:36

እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
37:37

አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡

🔊 📋 🔍
37:38

እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡

🔊 📋 🔍
37:39

ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡

🔊 📋 🔍
37:40

ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡

🔊 📋 🔍
37:41

እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:42

ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤

🔊 📋 🔍
37:43

በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡

🔊 📋 🔍
37:44

ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
37:45

ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡

🔊 📋 🔍
37:46

ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡

🔊 📋 🔍
37:47

በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡

🔊 📋 🔍
37:48

እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:49

እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:50

የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:51

ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡

🔊 📋 🔍
37:52

«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡

🔊 📋 🔍
37:53

«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡

🔊 📋 🔍
37:54

እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡

🔊 📋 🔍
37:55

ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡

🔊 📋 🔍
37:56

ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
37:57

«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»

🔊 📋 🔍
37:58

(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?

🔊 📋 🔍
37:59

«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
37:60

ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:61

ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡

🔊 📋 🔍
37:62

በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?

🔊 📋 🔍
37:63

እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡

🔊 📋 🔍
37:64

እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡

🔊 📋 🔍
37:65

እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡

🔊 📋 🔍
37:66

እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:67

ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:68

ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:69

እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡

🔊 📋 🔍
37:70

እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡

🔊 📋 🔍
37:71

ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡

🔊 📋 🔍
37:72

በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡

🔊 📋 🔍
37:73

የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡

🔊 📋 🔍
37:74

ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

🔊 📋 🔍
37:75

ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!

🔊 📋 🔍
37:76

እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡

🔊 📋 🔍
37:77

ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤

🔊 📋 🔍
37:78

በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡

🔊 📋 🔍
37:79

«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»

🔊 📋 🔍
37:80

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

🔊 📋 🔍
37:81

እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡

🔊 📋 🔍
37:82

ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡

🔊 📋 🔍
37:83

ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:84

ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡

🔊 📋 🔍
37:85

«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡

🔊 📋 🔍
37:86

«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?

🔊 📋 🔍
37:87

«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡

🔊 📋 🔍
37:88

በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡

🔊 📋 🔍
37:89

«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡

🔊 📋 🔍
37:90

ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡

🔊 📋 🔍
37:91

ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»

🔊 📋 🔍
37:92

«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»

🔊 📋 🔍
37:93

በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡

🔊 📋 🔍
37:94

ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡

🔊 📋 🔍
37:95

አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»

🔊 📋 🔍
37:96

«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»

🔊 📋 🔍
37:97

«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:98

በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:99

አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»

🔊 📋 🔍
37:100

ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡

🔊 📋 🔍
37:101

ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:102

ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡

🔊 📋 🔍
37:103

ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡

🔊 📋 🔍
37:104

ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!

🔊 📋 🔍
37:105

ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

🔊 📋 🔍
37:106

ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:107

በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:108

በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡

🔊 📋 🔍
37:109

ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡

🔊 📋 🔍
37:110

እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

🔊 📋 🔍
37:111

እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:112

በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡

🔊 📋 🔍
37:113

በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡

🔊 📋 🔍
37:114

በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡

🔊 📋 🔍
37:115

እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡

🔊 📋 🔍
37:116

ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡

🔊 📋 🔍
37:117

በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:118

ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:119

በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:120

ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡

🔊 📋 🔍
37:121

እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

🔊 📋 🔍
37:122

ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:123

ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:124

ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?

🔊 📋 🔍
37:125

በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?

🔊 📋 🔍
37:126

አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?

🔊 📋 🔍
37:127

አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:128

ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡

🔊 📋 🔍
37:129

በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡

🔊 📋 🔍
37:130

ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡

🔊 📋 🔍
37:131

እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡

🔊 📋 🔍
37:132

እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:133

ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:134

እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡

🔊 📋 🔍
37:135

(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡

🔊 📋 🔍
37:136

ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡

🔊 📋 🔍
37:137

እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡

🔊 📋 🔍
37:138

በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?

🔊 📋 🔍
37:139

ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
37:140

ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡

🔊 📋 🔍
37:141

ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡

🔊 📋 🔍
37:142

እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡

🔊 📋 🔍
37:143

እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤

🔊 📋 🔍
37:144

እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
37:145

እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡

🔊 📋 🔍
37:146

በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡

🔊 📋 🔍
37:147

ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:148

አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:149

(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»

🔊 📋 🔍
37:150

ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?

🔊 📋 🔍
37:151

ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-

🔊 📋 🔍
37:152

«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:153

በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?

🔊 📋 🔍
37:154

ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!

🔊 📋 🔍
37:155

አትገነዘቡምን?

🔊 📋 🔍
37:156

ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?

🔊 📋 🔍
37:157

«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡

🔊 📋 🔍
37:158

በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡

🔊 📋 🔍
37:159

አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡

🔊 📋 🔍
37:160

ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡

🔊 📋 🔍
37:161

እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤

🔊 📋 🔍
37:162

በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡

🔊 📋 🔍
37:163

ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡

🔊 📋 🔍
37:164

(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡

🔊 📋 🔍
37:165

እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡

🔊 📋 🔍
37:166

እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡

🔊 📋 🔍
37:167

እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-

🔊 📋 🔍
37:168

«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤

🔊 📋 🔍
37:169

«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»

🔊 📋 🔍
37:170

ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:171

(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡

🔊 📋 🔍
37:172

እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:173

ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:174

ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡

🔊 📋 🔍
37:175

እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:176

በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?

🔊 📋 🔍
37:177

በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!

🔊 📋 🔍
37:178

እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡

🔊 📋 🔍
37:179

ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡

🔊 📋 🔍
37:180

የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡

🔊 📋 🔍
37:181

በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤

🔊 📋 🔍
37:182

ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡

🔊 📋 🔍
00:00 / 00:00
Seraphinite AcceleratorOptimized by Seraphinite Accelerator
Turns on site high speed to be attractive for people and search engines.