...

Amharic Quran

አጥ ጡር

بسم الله الرحمن الرحيم

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

52:1

በጡር (ጋራ) እምላለሁ፡፡

🔊 📋 🔍
52:2

በተጻፈው መጽሐፍም፡፡

🔊 📋 🔍
52:3

በተዘረጋ ብራና ላይ፤ (በተጻፈው)፡፡

🔊 📋 🔍
52:4

በደመቀው ቤትም፡፡

🔊 📋 🔍
52:5

ከፍ በተደረገው ጣራም፡፡

🔊 📋 🔍
52:6

በተመላው ባሕርም እምላለሁ፡፡

🔊 📋 🔍
52:7

የጌታህ ቅጣት በእርግጥ ወዳቂ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡

🔊 📋 🔍
52:8

ለእርሱ ምንም ገፍታሪ የለውም፡፡

🔊 📋 🔍
52:9

ሰማይ ብርቱ መዞርን በምትዞርበት ቀን (ይኾናል)፡፡

🔊 📋 🔍
52:10

ተራራዎችም መኼድን በሚኼዱበት (ቀን)፡፡

🔊 📋 🔍
52:11

ለአስተባባዮችም ያን ጊዜ ወዮላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
52:12

ለእነዚያ እነርሱ በውሸት ውስጥ የሚጫወቱ ለኾኑት፡፡

🔊 📋 🔍
52:13

ወደ ገሀነም እሳት በኀይል መግገፍተርን በሚግገፈተሩበት ቀን፡፡

🔊 📋 🔍
52:14

ይህቺ ያቺ በእርሷ ታስተባብሉባት የነበራችሁት እሳት ናት፡፡

🔊 📋 🔍
52:15

ይህ (ፊት ትሉ እንደነበራችሁት) ድግምት ነውን? ወይስ እናንተ አታዩምን?

🔊 📋 🔍
52:16

ግቧት ታገሱም ወይም አትታገሡ በእናንተ ላይ እኩል ነው፡፡ የምትምመነዱት ትሠሩት የነበራችሁትን (ፍዳ) ብቻ ነው (ይባላሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
52:17

አላህን ፈሪዎቹ በእርግጥ በገነቶችና በጸጋ ውስጥ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
52:18

ጌታቸው በሰጣቸው ጸጋ ተደሳቾች ኾነው (በገነት ውስጥ ናቸው)፡፡ የገሀነምንም ስቃይ ጌታቸው ጠበቃቸው፡፡

🔊 📋 🔍
52:19

«ትሠሩት በነበራችሁት ምክንያት ተደሳቾች ኾናችሁ ብሉ፤ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
52:20

በተደረደሩ አልጋዎች ላይ ተደጋፊዎች ኾነው (በገነት ይኖራሉ)፡፡ ዓይናማዎች በኾኑ ነጫጭ ሴቶችም እናጠናዳቸዋለን፡፡

🔊 📋 🔍
52:21

እነዚያም ያመኑትና ዝርያቸውም በእምነት የተከተለቻቸው ዝርያቸውን በእነርሱ እናስጠጋለን፡፡ ከሥራቸውም ምንም አናጎድልባቸውም፡፡ ሰው ሁሉ በሠራው ሥራ ተያዢ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
52:22

ከሚሹትም ሁሉ እሸትንና ስጋን እንጨምርላቸዋለን፡፡

🔊 📋 🔍
52:23

በውስጧ መጠጥን ይሰጣጣሉ፡፡ በውስጧ ውድቅ ንግግርና መውወንጀልም የለም፡፡

🔊 📋 🔍
52:24

ለነርሱም የኾኑ ወጣቶች ልክ የተሸፈነ ሉል መስለው በእነርሱ ላይ (ለማሳለፍ) ይዘዋወራሉ፡፡

🔊 📋 🔍
52:25

የሚጠያየቁ ኾነውም ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይዞራል፡፡

🔊 📋 🔍
52:26

«እኛ ፊት በቤተሰቦቻችን ውስጥ (ከቅጣት) ፈሪዎች ነበርን» ይላሉ፡፡

🔊 📋 🔍
52:27

«አላህም በእኛ ላይ ለገሰ፡፡ የመርዛም እሳት ቅጣትንም ጠበቀን፡፡

🔊 📋 🔍
52:28

«እኛ ከዚህ በፊት እንለምነው ነበርን፡፡ እነሆ እርሱ በጎ ዋይ አዛኝ ነውና» (ይላሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
52:29

(ሰዎችን) አስታውስም፡፡ አንተም በጌታህ ጸጋ ምክንያት ጠንቋይም ዕብድም አይደለህም፡፡

🔊 📋 🔍
52:30

ይልቁንም የሞትን አደጋ በእርሱ የምንጠባበቅበት የኾነ ባለ ቅኔ ነው ይላሉን?

🔊 📋 🔍
52:31

«ተጠባበቁ፤ እኔም ከእናንተ ጋር ከሚጠባበቁት ነኝ» በላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
52:32

አእምሮዎቻቸው በዚህ ያዟቸዋልን? አይደለም በእውነቱ እነርሱ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦች ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
52:33

ወይም «ቀጠፈው ይላሉን?» አይደለም፤ በእውነቱ አያምኑም፡፡

🔊 📋 🔍
52:34

እውነተኞችም ቢኾኑ መሰሉ የኾነን ንግግር ያምጡ፡፡

🔊 📋 🔍
52:35

ወይስ ያለ አንዳች (ፈጣሪ) ተፈጠሩን? ወይስ እነርሱ ፈጣሪዎች ናቸውን?

🔊 📋 🔍
52:36

ወይስ ሰማያትንና ምድርን ፈጠሩን? አይደለም አያረጋግጡም፡፡

🔊 📋 🔍
52:37

ወይስ የጌታህ ግምጃ ቤቶች እነርሱ ዘንድ ናቸውን? ወይስ እነርሱ አሸናፊዎች ናቸውን?

🔊 📋 🔍
52:38

ወይስ ለእነርሱ በእርሱ ላይ (ከሰማይ) የሚያዳምጡበት መሰላል አላቸውን? አድማጫቸውም (ሰማሁ ቢል) ግልጽን አስረጅ ያምጣ፡፡

🔊 📋 🔍
52:39

ወይስ ለእርሱ ሴቶች ልጆች አሉትን? ለእናንተም ወንዶች ልጆች አሏችሁን?

🔊 📋 🔍
52:40

ወይስ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳው የተከበዱ ናቸውን?

🔊 📋 🔍
52:41

ወይስ ሩቁ ምስጢር እነርሱ ዘንድ ነውን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?

🔊 📋 🔍
52:42

ወይስ ተንኮልን (ባንተ) ይሻሉን? እነዚያም የካዱት እነርሱ በተንኮል ተሸናፊዎች ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
52:43

ወይስ ለእነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ አላቸውን? አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ፡፡

🔊 📋 🔍
52:44

ከሰማይም ቁራጭን (በእነርሱ ላይ) ወዳቂ ኾኖ ቢያዩ ኖሮ «ይህ የተደራረበ ደመና ነው» ይሉ ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
52:45

ያንንም በእርሱ የሚግገደሉበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡

🔊 📋 🔍
52:46

ተንኮላቸው ከእነርሱ ምንንም የማይጠቅማቸውንና እነርሱም የማይርረዱበትን ቀን (እስከ ሚገናኙ ተዋቸው)፡፡

🔊 📋 🔍
52:47

ለእነዚያ ለበደሉትም ከዚህ ሌላ ቅርብ ቅጣት አልላቸው፡፡ ግን አብዛኛዎቻቸው አያውቁም፡፡

🔊 📋 🔍
52:48

ለጌታህ ፍርድም ታገሥ፡፡ አንተ በጥበቃችን ውስጥ ነህና፡፡ ጌታህንም በምትነሳ ጊዜ ከማመስገን ጋር አወድሰው፡፡

🔊 📋 🔍
52:49

ከሌሊቱም አወድሰው፡፡ በከዋክብት መዳበቂያ ጊዜም (ንጋት ላይ አወድሰው)፡፡

🔊 📋 🔍
00:00 / 00:00
Seraphinite AcceleratorOptimized by Seraphinite Accelerator
Turns on site high speed to be attractive for people and search engines.