...

Amharic Quran

አል ቀለም

بسم الله الرحمن الرحيم

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

68:1

ነ.(ኑን)፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡

🔊 📋 🔍
68:2

አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡

🔊 📋 🔍
68:3

ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡

🔊 📋 🔍
68:4

አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡

🔊 📋 🔍
68:5

ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡

🔊 📋 🔍
68:6

ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡

🔊 📋 🔍
68:7

ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
68:8

ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡

🔊 📋 🔍
68:9

ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡

🔊 📋 🔍
68:10

ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡

🔊 📋 🔍
68:11

ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡

🔊 📋 🔍
68:12

ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤

🔊 📋 🔍
68:13

ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡

🔊 📋 🔍
68:14

የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡

🔊 📋 🔍
68:15

በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

🔊 📋 🔍
68:16

በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡

🔊 📋 🔍
68:17

እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡

🔊 📋 🔍
68:18

(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡

🔊 📋 🔍
68:19

እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡

🔊 📋 🔍
68:20

እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡

🔊 📋 🔍
68:21

ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡

🔊 📋 🔍
68:22

«ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡

🔊 📋 🔍
68:23

እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡

🔊 📋 🔍
68:24

ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡

🔊 📋 🔍
68:25

(ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡

🔊 📋 🔍
68:26

(ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡

🔊 📋 🔍
68:27

«ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡

🔊 📋 🔍
68:28

ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
68:29

«ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡

🔊 📋 🔍
68:30

የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡

🔊 📋 🔍
68:31

«ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡

🔊 📋 🔍
68:32

«ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
68:33

ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡

🔊 📋 🔍
68:34

ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡

🔊 📋 🔍
68:35

ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?

🔊 📋 🔍
68:36

ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡

🔊 📋 🔍
68:37

በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?

🔊 📋 🔍
68:38

በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)

🔊 📋 🔍
68:39

ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?

🔊 📋 🔍
68:40

በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡

🔊 📋 🔍
68:41

ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡

🔊 📋 🔍
68:42

ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡

🔊 📋 🔍
68:43

ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡

🔊 📋 🔍
68:44

በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡

🔊 📋 🔍
68:45

እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡

🔊 📋 🔍
68:46

በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?

🔊 📋 🔍
68:47

ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?

🔊 📋 🔍
68:48

ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡

🔊 📋 🔍
68:49

ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
68:50

ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡

🔊 📋 🔍
68:51

እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡

🔊 📋 🔍
68:52

ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡

🔊 📋 🔍
00:00 / 00:00
Seraphinite AcceleratorOptimized by Seraphinite Accelerator
Turns on site high speed to be attractive for people and search engines.