...

Amharic Quran

ዐበሰ

بسم الله الرحمن الرحيم

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

80:1

ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡

🔊 📋 🔍
80:2

ዕውሩ ስለ መጣው፡፡

🔊 📋 🔍
80:3

ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡

🔊 📋 🔍
80:4

ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡

🔊 📋 🔍
80:5

የተብቃቃው ሰውማ፤

🔊 📋 🔍
80:6

አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡

🔊 📋 🔍
80:7

ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡

🔊 📋 🔍
80:8

እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤

🔊 📋 🔍
80:9

እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤

🔊 📋 🔍
80:10

አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡

🔊 📋 🔍
80:11

ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡

🔊 📋 🔍
80:12

የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡

🔊 📋 🔍
80:13

በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
80:14

ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡

🔊 📋 🔍
80:15

በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡

🔊 📋 🔍
80:16

የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡

🔊 📋 🔍
80:17

ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?

🔊 📋 🔍
80:18

(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)

🔊 📋 🔍
80:19

ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡

🔊 📋 🔍
80:20

ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡

🔊 📋 🔍
80:21

ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡

🔊 📋 🔍
80:22

ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡

🔊 📋 🔍
80:23

በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡

🔊 📋 🔍
80:24

ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡

🔊 📋 🔍
80:25

እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡

🔊 📋 🔍
80:26

ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤

🔊 📋 🔍
80:27

በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤

🔊 📋 🔍
80:28

ወይንንም፤ እርጥብ ያበቀልን፤

🔊 📋 🔍
80:29

የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤

🔊 📋 🔍
80:30

ጭፍቆች አትክልቶችንም፤

🔊 📋 🔍
80:31

ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡

🔊 📋 🔍
80:32

ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡

🔊 📋 🔍
80:33

አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
80:34

ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤

🔊 📋 🔍
80:35

ከናቱም ካባቱም፤

🔊 📋 🔍
80:36

ከሚስቱም ከልጁም፤

🔊 📋 🔍
80:37

ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡

🔊 📋 🔍
80:38

ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤

🔊 📋 🔍
80:39

ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
80:40

ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤

🔊 📋 🔍
80:41

ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤

🔊 📋 🔍
80:42

እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
00:00 / 00:00
Seraphinite AcceleratorOptimized by Seraphinite Accelerator
Turns on site high speed to be attractive for people and search engines.