...

Amharic Quran

አት ተክዊር

بسم الله الرحمن الرحيم

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

81:1

ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:2

ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:3

ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:4

የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:5

እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:6

ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:7

ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:8

በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:9

በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤

🔊 📋 🔍
81:10

ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:11

ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:12

ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:13

ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:14

ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤

🔊 📋 🔍
81:15

ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡

🔊 📋 🔍
81:16

ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡

🔊 📋 🔍
81:17

በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
81:18

በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡

🔊 📋 🔍
81:19

እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡

🔊 📋 🔍
81:20

የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡

🔊 📋 🔍
81:21

በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡

🔊 📋 🔍
81:22

ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡

🔊 📋 🔍
81:23

በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡

🔊 📋 🔍
81:24

እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡

🔊 📋 🔍
81:25

እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡

🔊 📋 🔍
81:26

ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?

🔊 📋 🔍
81:27

እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

🔊 📋 🔍
81:28

ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡

🔊 📋 🔍
81:29

የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡

🔊 📋 🔍
00:00 / 00:00
Seraphinite AcceleratorOptimized by Seraphinite Accelerator
Turns on site high speed to be attractive for people and search engines.