...

Amharic Quran

አል ኢንፌጣር

بسم الله الرحمن الرحيم

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

82:1

ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
82:2

ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
82:3

ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
82:4

መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
82:5

ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡

🔊 📋 🔍
82:6

አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?

🔊 📋 🔍
82:7

በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡

🔊 📋 🔍
82:8

በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡

🔊 📋 🔍
82:9

ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡

🔊 📋 🔍
82:10

በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤

🔊 📋 🔍
82:11

የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡

🔊 📋 🔍
82:12

የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡

🔊 📋 🔍
82:13

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
82:14

ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
82:15

በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡

🔊 📋 🔍
82:16

እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡

🔊 📋 🔍
82:17

የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

🔊 📋 🔍
82:18

ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

🔊 📋 🔍
82:19

(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
00:00 / 00:00
Seraphinite AcceleratorOptimized by Seraphinite Accelerator
Turns on site high speed to be attractive for people and search engines.