...

Amharic Quran

አል ሙጠፊፊን

بسم الله الرحمن الرحيم

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

83:1

ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
83:2

ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡

🔊 📋 🔍
83:3

ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡

🔊 📋 🔍
83:4

እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?

🔊 📋 🔍
83:5

በታላቁ ቀን፡፡

🔊 📋 🔍
83:6

ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡

🔊 📋 🔍
83:7

በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
83:8

ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

🔊 📋 🔍
83:9

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
83:10

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
83:11

ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡

🔊 📋 🔍
83:12

በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡

🔊 📋 🔍
83:13

አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

🔊 📋 🔍
83:14

ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡

🔊 📋 🔍
83:15

ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
83:16

ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
83:17

ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡

🔊 📋 🔍
83:18

በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
83:19

ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

🔊 📋 🔍
83:20

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
83:21

ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡

🔊 📋 🔍
83:22

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
83:23

በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡

🔊 📋 🔍
83:24

በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡

🔊 📋 🔍
83:25

ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡

🔊 📋 🔍
83:26

ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡

🔊 📋 🔍
83:27

መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡

🔊 📋 🔍
83:28

ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡

🔊 📋 🔍
83:29

እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡

🔊 📋 🔍
83:30

በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
83:31

ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
83:32

ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
83:33

በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡

🔊 📋 🔍
83:34

ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡

🔊 📋 🔍
83:35

በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
83:36

ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
00:00 / 00:00
Seraphinite AcceleratorOptimized by Seraphinite Accelerator
Turns on site high speed to be attractive for people and search engines.