...

Amharic Quran

አል ኢንሺቃቅ

بسم الله الرحمن الرحيم

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

84:1

ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
84:2

ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤

🔊 📋 🔍
84:3

ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
84:4

በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
84:5

ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡

🔊 📋 🔍
84:6

አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡

🔊 📋 🔍
84:7

መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤

🔊 📋 🔍
84:8

በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡

🔊 📋 🔍
84:9

ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡

🔊 📋 🔍
84:10

መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤

🔊 📋 🔍
84:11

(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡

🔊 📋 🔍
84:12

የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡

🔊 📋 🔍
84:13

እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡

🔊 📋 🔍
84:14

እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡

🔊 📋 🔍
84:15

አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡

🔊 📋 🔍
84:16

አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡

🔊 📋 🔍
84:17

በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤

🔊 📋 🔍
84:18

በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡

🔊 📋 🔍
84:19

ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡

🔊 📋 🔍
84:20

የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?

🔊 📋 🔍
84:21

በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?)

🔊 📋 🔍
84:22

በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡

🔊 📋 🔍
84:23

አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
84:24

በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡

🔊 📋 🔍
84:25

ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
00:00 / 00:00
Seraphinite AcceleratorOptimized by Seraphinite Accelerator
Turns on site high speed to be attractive for people and search engines.