...

Amharic Quran

አል ፈጅር

بسم الله الرحمن الرحيم

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

89:1

በጎህ እምላለሁ፡፡

🔊 📋 🔍
89:2

በዐሥር ሌሊቶችም፡፡

🔊 📋 🔍
89:3

በጥንዱም በነጠላውም፡፡

🔊 📋 🔍
89:4

በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡

🔊 📋 🔍
89:5

በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?

🔊 📋 🔍
89:6

ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?

🔊 📋 🔍
89:7

በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡

🔊 📋 🔍
89:8

በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡

🔊 📋 🔍
89:9

በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡

🔊 📋 🔍
89:10

በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡

🔊 📋 🔍
89:11

በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡

🔊 📋 🔍
89:12

በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)

🔊 📋 🔍
89:13

በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡

🔊 📋 🔍
89:14

ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡

🔊 📋 🔍
89:15

ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡

🔊 📋 🔍
89:16

በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡

🔊 📋 🔍
89:17

ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡

🔊 📋 🔍
89:18

ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡

🔊 📋 🔍
89:19

የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡

🔊 📋 🔍
89:20

ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡

🔊 📋 🔍
89:21

ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
89:22

መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ትዕዛዙ) በመጣ ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
89:23

ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?

🔊 📋 🔍
89:24

«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡

🔊 📋 🔍
89:25

በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡

🔊 📋 🔍
89:26

የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡

🔊 📋 🔍
89:27

(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!

🔊 📋 🔍
89:28

«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡

🔊 📋 🔍
89:29

«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡

🔊 📋 🔍
89:30

ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡

🔊 📋 🔍
00:00 / 00:00
Seraphinite AcceleratorOptimized by Seraphinite Accelerator
Turns on site high speed to be attractive for people and search engines.