አሽ ሸምስ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡
91:1
በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
🔊 📋 🔍
91:2
በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
🔊 📋 🔍
91:3
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
🔊 📋 🔍
91:4
በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
🔊 📋 🔍
91:5
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
🔊 📋 🔍
91:6
በምድሪቱም በዘረጋትም፤
🔊 📋 🔍
91:7
በነፍስም ባስተካከላትም፤
🔊 📋 🔍
91:8
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
🔊 📋 🔍
91:9
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
🔊 📋 🔍
91:10
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
🔊 📋 🔍
91:11
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
🔊 📋 🔍
91:12
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
🔊 📋 🔍
91:13
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
🔊 📋 🔍
91:14
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
🔊 📋 🔍
91:15
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡
🔊 📋 🔍
▶