...

Amharic Quran

አል ሒጅር

بسم الله الرحمن الرحيم

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው፡፡

15:1

አ.ለ.ረ (አሊፍ ላም ራ) ይህች (አናቅጽ) ከመጽሐፉ አንቀጾችና ገላጭ ከኾነው ቁርኣን ናት፡፡

🔊 📋 🔍
15:2

እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ ቀን) ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡

🔊 📋 🔍
15:3

ተዋቸው ይብሉ፤ ይጠቀሙም፡፡ ተስፋም ያዘናጋቸው፡፡ በእርግጥም (መጥፎ ፍጻሜያቸውን) ያውቃሉ፡፡

🔊 📋 🔍
15:4

ማንኛይቱንም ከተማ ለእርሷ የተወሰነ መጽሐፍ (ጊዜያት) ያላት ኾና እንጂ አላጠፋንም፡፡

🔊 📋 🔍
15:5

ማንኛይቱም ሕዝብ ጊዜዋን ምንም አትቀድምም፡፡ (ከእርሱ) አይቆዩምም፡፡

🔊 📋 🔍
15:6

«አንተ ያ በእርሱ ላይ ቁርኣን የተወረደለት ሆይ! አንተ በእርግጥ ዕብድ ነህ» አሉም፡፡

🔊 📋 🔍
15:7

«ከእውነተኞቹ እንደ ኾንክ በመላእክት (መስካሪ) ለምን አትመጣንም» (አሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
15:8

መላእክትን በእውነት (በቅጣት) እንጂ አናወርድም፡፡ ያን ጊዜም የሚቆዩ አይደሉም፡፡

🔊 📋 🔍
15:9

እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው፡፡ እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን፡፡

🔊 📋 🔍
15:10

ከአንተም በፊት በነበሩት በመጀመሪያዎቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልክተኞችን) በእርግጥ ልከናል፡፡

🔊 📋 🔍
15:11

ማንኛውም መልእክተኛ በእርሱ የሚያላግጡበት ኾነው እንጅ አይመጣቸውም ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
15:12

እንደዚሁ (ማስተባበልን) በአመጸኞቹ ልቦች ውስጥ እናገባዋለን፡፡

🔊 📋 🔍
15:13

በእርሱ አያምኑበትም፡፡ የቀድሞዎቹም ድርጊት በእርግጥ አልፋለች፤ (እንደጠፉ ይጠፋሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
15:14

በእነርሱም ላይ ከሰማይ ደጃፍን በከፈትንላቸውና በእርሱ ሲወጡ በዋሉ ኖሮ፤

🔊 📋 🔍
15:15

«የተዘጉት ዓይኖቻችን ናቸው፡፡ እንዲያውም እኛ የተደገመብን ሰዎች ነን» ባሉ ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
15:16

በሰማይም ላይ ቡርጆችን በእርግጥ አድርገናል፡፡ ለተመልካቾችም (በከዋክብት) አጊጠናታል፡፡

🔊 📋 🔍
15:17

ከተባረረ ሰይጣንም ሁሉ ጠብቀናታል፡፡

🔊 📋 🔍
15:18

ግን (ወሬ) መስማትን የሚሰርቅ ወዲየውኑ አብሪ ችቦ ይከተለዋል፡፡ (ያቃጥለዋል)፡፡

🔊 📋 🔍
15:19

ምድርንም ዘረጋናት፡፡ በውስጧም ኮረብታዎችን ጣልናባት፡፡ በውስጧም (የተለካን) በቃይ ሁሉ አበቀልንባት፡፡

🔊 📋 🔍
15:20

በእርሷም ውስጥ ለእናንተ መኖሪያዎችንና ለእርሱ መጋቢዎቹ ያልኾናችሁትንም (እንስሳትን) አደረግንላችሁ፡፡

🔊 📋 🔍
15:21

መካዚኖቹም (መክፈቻቸው) እኛ ዘንድ ያልሆነ ምንም ነገር የለም፡፡ በተወሰነም ልክ እንጂ አናወርደውም፡፡

🔊 📋 🔍
15:22

ነፋሶችንም (ደመናን) ተሸካሚዎች አድርገን ላክን፡፡ ከሰማይም (ከደመና) ዝናብን አወረድን፡፡ እርሱንም አጠጣናችሁ፡፡ እናንተም ለእርሱ አድላቢዎች አይደላችሁም፡፡

🔊 📋 🔍
15:23

እኛም ሕያው የምናደርግና የምንገድል እኛው ብቻ ነን፡፡ እኛም (ፍጡርን ሁሉ ) የምንወርስ (ቀሪ) ነን፡፡

🔊 📋 🔍
15:24

ከእናንተም ተቀዳሚዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ ወደ ኋላም ቀሪዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡

🔊 📋 🔍
15:25

ጌታህም እርሱ ይሰበስባችኋል፡፡ እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ ነውና፡፡

🔊 📋 🔍
15:26

ሰውንም ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጥቁር ጭቃ በእርግጥ ፈጠርነው፡፡

🔊 📋 🔍
15:27

ጃንንም (ከሰው) በፊት ከእሳት ነበልባል ፈጠርነው፡፡

🔊 📋 🔍
15:28

ጌታህም ለመላእክት ባለጊዜ (አስታውስ)፡፡ እኔ ሰውን ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጭቃ እፈጥራለሁ፡፡

🔊 📋 🔍
15:29

(ፍጥረቱን) ባስተካከልኩትና በውስጡ ከመንፈሴ በነፋሁበትም ጊዜ ለእርሱ ሰጋጆች ኾናችሁ ውደቁ፡፡

🔊 📋 🔍
15:30

መላእክትም መላውም ተሰብስበው ሰገዱ፡፡

🔊 📋 🔍
15:31

ኢብሊስ (ዲያብሎስ) ብቻ ሲቀር፡፡ ከሰጋጆቹ ጋር ከመኾን እንቢ አለ፡፡

🔊 📋 🔍
15:32

(አላህም) «ኢብሊስ ሆይ! ከሰጋጆቹ ጋር የማትኾን ላንተ ምን ምክንያት አለህ» አለው፡፡

🔊 📋 🔍
15:33

«ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከግም ጭቃ ለፈጠርከው ሰው ልሰግድ አይገባኝም» አለ፡፡

🔊 📋 🔍
15:34

(አላህ) አለው «ከርሷም ውጣ፡፡ አንተ የተባረርክ እርጉም ነህና፡፡»

🔊 📋 🔍
15:35

«ባንተ ላይም እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ እርግማን አለብህ፡፡»

🔊 📋 🔍
15:36

«ጌታዬ ሆይ! እንግዲውያስ (ሰዎች) እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝ» አለ፡፡

🔊 📋 🔍
15:37

(አላህም) አለ «አንተ ከሚቆዩት ነህ፡፡

🔊 📋 🔍
15:38

«እስከታወቀው ወቅት ቀን ድረስ፡፡»

🔊 📋 🔍
15:39

(ኢብሊስ) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔን በማጥመምህ ይኹንብኝ ለነርሱ በምድር ላይ (ኀጢአትን) እሸልምላቸዋለሁ፡፡ ሁሉንም አጠማቸዋለሁም፡፡»

🔊 📋 🔍
15:40

«ከነርሱ ፍጹሞቹ ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ፡፡»

🔊 📋 🔍
15:41

(አላህም) አለ «ይህ በእኔ ላይ (መጠበቁ የተገባ) ቀጥተኛ መንገድ ነው፡፡»

🔊 📋 🔍
15:42

«እነሆ ባሮቼ በእነሱ ላይ ላንተ ስልጣን የለህም፡፡ ከጠማሞቹ የተከተለህ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡»

🔊 📋 🔍
15:43

«ገሀነምም (ለርሱና ለተከተሉት) ለመላውም በእርግጥ ቀጠሯቸው ናት፡፡

🔊 📋 🔍
15:44

«ለእርሷ ሰባት ደጃፎች አሏት፡፡ ለየደጀፉም ሁሉ ከእነሱ የተከፈለ ፋንታ አለ፡፡

🔊 📋 🔍
15:45

«እነዚያ (ከኀጢአት) የተጠነቀቁት በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:46

«ጸጥተኞች ኾናችሁ በሰላም ግቧት (ይባላሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
15:47

«ባልጋዎችም ላይ ፊት ለፊት የሚቅጣጩ ወንድማማቾች ኾነው በደረቶቻቸው ውስጥ ከቂም ያለውን ሁሉ እናስወግዳለን፡፡

🔊 📋 🔍
15:48

«በእርሷም ውስጥ ድካም አይነካቸውም፡፡ እነሱም ከእርሷ የሚወጡ አይደሉም፡፡»

🔊 📋 🔍
15:49

ባሮቼን እኔ መሓሪው አዛኙ እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:50

ቅጣቴም እርሱ አሳማሚ ቅጣት መኾኑን (ንገራቸው)፡፡

🔊 📋 🔍
15:51

ከኢብራሂም እንግዶችም (ወሬ) ንገራቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:52

በእርሱ ላይ በገቡና ሰላም ባሉት ጊዜ የኾነውን (አስታውስ)፡፡ (እርሱም) «እኛ ከእናንተ ፈሪዎች ነን» አላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:53

«አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ እናበስርሃለን» አሉት፡፡

🔊 📋 🔍
15:54

«እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ» አለ፡፡

🔊 📋 🔍
15:55

«በእውነት አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን» አሉ፡፡

🔊 📋 🔍
15:56

«ከጠማማዎችም በስተቀር ከጌታው እዝነት ተስፋን የሚቆርጥ ማነው» አለ፡፡

🔊 📋 🔍
15:57

«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ኧረ ለመኾኑ ነገራችሁ ምንድን ነው» አለ፡፡

🔊 📋 🔍
15:58

«እኛ አመጸኞች ወደ ኾኑ ሕዝቦች ተልከናል» አሉት፡፡

🔊 📋 🔍
15:59

«የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ፡፡ (እነርሱን) እኛ ሁላቸውንም በእርግጥ የምናድናቸው ነን፡፡

🔊 📋 🔍
15:60

«ሚስቱ ብቻ ስትቀር፡፡ እርሷን (በቅጣቱ ውስጥ) ከሚቀሩት መኾኗን ወሰነናል» (አሉ)፡፡

🔊 📋 🔍
15:61

መልክተኞቹም የሉጥን ቤተሰቦች በመጡባቸው ጊዜ፤

🔊 📋 🔍
15:62

(ሉጥ) «እናንተ የተሳታችሁ ሕዝቦች ናችሁ» አላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:63

«አይደለም እኛ ሕዝቦችህ በርሱ ይጠራጠሩበት በነበሩት ቅጣት መጣንህ» አሉት፡፡

🔊 📋 🔍
15:64

«እውነትንም ይዘን መጣንህ፡፡ እኛም በእርግጥ እውነተኞች ነን፡፡

🔊 📋 🔍
15:65

ከቤተሰብህም ጋር በሌሊቱ ከፊል ኺድ፡፡ ከኋላቸውም ተከተል፡፡ ከእናንተም አንድም ሰው ወደ ኋላው አይገላመጥ፡፡ ወደ ታዘዛችሁበትም ስፍራ እለፉ» (አሉት)፡፡

🔊 📋 🔍
15:66

ወደርሱም ያንን ትእዛዝ አወረድን፡፡ (እርሱም) የእነዚህ (ሕዝቦች) መጨረሻ ያነጉ ሲኾኑ (ሥራቸው) መቆረጥ ነው፡፡

🔊 📋 🔍
15:67

የከተማይቱም ሰዎች የሚበሳሰሩ ኾነው መጡ፡፡

🔊 📋 🔍
15:68

(ሉጥም) አለ «እነዚህ እንግዶቼ ናቸውና አታጋልጡኝ፡፡

🔊 📋 🔍
15:69

«አላህንም ፍሩ፤ አታሳፍሩኝም፡፡»

🔊 📋 🔍
15:70

«ከዓለማት (ማንንም እንዳታስተናግድ) አልከለከልንህምን» አሉት፡፡

🔊 📋 🔍
15:71

(ሉጥም) «እነኝህ ሴቶች ልጆቼ ናቸው፡፡ ሠሪዎች ብትኾኑ (አግቧቸው)» አለ፡፡

🔊 📋 🔍
15:72

በዕድሜህ እንምላለን እነሱ በእርግጥ በስከራቸው ውስጥ ይዋልላሉ፡፡

🔊 📋 🔍
15:73

ጩኸቲቱም ፀሐይ የወጣችባቸው ሲኾኑ ያዘቻቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:74

ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:75

በዚህ ውስጥ ለተመልካቾች በእርግጥ መገምገሚያዎች አሉበት፡፡

🔊 📋 🔍
15:76

እሷም (ከተማይቱ) በቀጥታ መንገድ ላይ ናት፡፡

🔊 📋 🔍
15:77

በዚህ ውስጥ በእርግጥ ለምእምናን መገሰጫ አለ፡፡

🔊 📋 🔍
15:78

እነሆ የአይከት ሰዎችም በእርግጥ በዳዮች ነበሩ፤

🔊 📋 🔍
15:79

ከነሱም ተበቀልን ሁለቱም (የሉጥና የአይከት ሕዝቦች ከተሞች) በእርግጥ በግልጽ መንገድ ላይ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:80

የሒጅርም ሰዎች መልክተኞቹን በእርግጥ አስተባበሉ፡፡

🔊 📋 🔍
15:81

ተዓምራታችንንም ሰጠናቸው፡፡ ከእርሷም ዘንጊዎች ነበሩ፡፡

🔊 📋 🔍
15:82

ከኮረብታዎችም ቤቶችን ጸጥተኞች ኾነው ይጠርቡ ነበር፡፡

🔊 📋 🔍
15:83

ያነጉም ሲኾኑ ጩኸት ያዘቻቸው፤ (ወደሙ)፡፡

🔊 📋 🔍
15:84

ይሠሩትም የነበሩት ሕንጻ ምንም አልጠቀማቸውም፡፡

🔊 📋 🔍
15:85

ሰማያትንና ምድርንም በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በእውነት እንጂ (በላግጣ) አልፈጠርንም፡፡ ሰዓቲቱም በእርግጥ መጪ ናት፡፡ መልካምንም ይቅርታ አድርግላቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:86

ጌታህ እርሱ (ያልነበረን) ፈጣሪው ዐዋቂው ነው፡፡

🔊 📋 🔍
15:87

ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትንና ታላቁንም ቁርኣን (በሙሉ) በእርግጥ ሰጠንህ፡፡

🔊 📋 🔍
15:88

ከእነርሱ (ከከሓዲዎች) ብዙዎችን ወገኖች በእርሱ ወደ አጣቀምንበት ጸጋ ዓይኖችህን አትዘርጋ፡፡ በእነሱም ላይ (ባያምኑ) አትዘን፡፡ ክንፍህንም ለምእምናን አለዝብ፡፡

🔊 📋 🔍
15:89

በልም «እኔ ግልጽ አስፈራሪው እኔ ነኝ፡፡»

🔊 📋 🔍
15:90

(ሰዎችን ለማገድ የመካን በሮች) በተከፋፈሉት ላይ እንደ አወረድነው (በኾነ ቅጣት አሰፈራሪያችሁ ነኝ በል)፡፡

🔊 📋 🔍
15:91

(እነርሱም) እነዚያ ቁርኣንንን ክፍልፍሎች ያደረጉ ናቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:92

በጌታህም እንምላለን፡፡ ሁላቸውንም እንጠይቃቸዋለን፤

🔊 📋 🔍
15:93

ይሠሩት ከነበሩት ነገር ሁሉ፡፡

🔊 📋 🔍
15:94

የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለጽ፡፡ አጋሪዎችንም ተዋቸው፡፡

🔊 📋 🔍
15:95

ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንሃል፡፡

🔊 📋 🔍
15:96

(እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፡፡ በእርግጥም (ፍጻሜያቸውን) ወደፊት ያውቃሉ፡፡

🔊 📋 🔍
15:97

አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መኾኑን በእርግጥ እናውቃለን፡፡

🔊 📋 🔍
15:98

ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው ከሰጋጆቹም ኹን፡፡

🔊 📋 🔍
15:99

እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡

🔊 📋 🔍
00:00 / 00:00
Seraphinite AcceleratorOptimized by Seraphinite Accelerator
Turns on site high speed to be attractive for people and search engines.