surah081

አት-ተክዊር የመጠቅለል ምዕራፍ
ድምፅ አቅራቢ (Qari)
የአጫዋች ሁነታ (Play Mode)
1
بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَـٰنِ الرَّحِيمِ

إِذَا الشَّمْسُ كُوِّرَتْ

ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤

2

وَإِذَا النُّجُومُ انكَدَرَتْ

ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤

3

وَإِذَا الْجِبَالُ سُيِّرَتْ

ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤

4

وَإِذَا الْعِشَارُ عُطِّلَتْ

የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤

5

وَإِذَا الْوُحُوشُ حُشِرَتْ

እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤

6

وَإِذَا الْبِحَارُ سُجِّرَتْ

ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤

7

وَإِذَا النُّفُوسُ زُوِّجَتْ

ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤

8

وَإِذَا الْمَوْءُودَةُ سُئِلَتْ

በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤

9

بِأَيِّ ذَنبٍ قُتِلَتْ

በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤

10

وَإِذَا الصُّحُفُ نُشِرَتْ

ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤

11

وَإِذَا السَّمَاءُ كُشِطَتْ

ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤

12

وَإِذَا الْجَحِيمُ سُعِّرَتْ

ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤

13

وَإِذَا الْجَنَّةُ أُزْلِفَتْ

ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤

14

عَلِمَتْ نَفْسٌ مَّا أَحْضَرَتْ

ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤

15

فَلَا أُقْسِمُ بِالْخُنَّسِ

ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡

16

الْجَوَارِ الْكُنَّسِ

ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡

17

وَاللَّيْلِ إِذَا عَسْعَسَ

በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤

18

وَالصُّبْحِ إِذَا تَنَفَّسَ

በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡

19

إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ

እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡

20

ذِي قُوَّةٍ عِندَ ذِي الْعَرْشِ مَكِينٍ

የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡

21

مُّطَاعٍ ثَمَّ أَمِينٍ

በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡

22

وَمَا صَاحِبُكُم بِمَجْنُونٍ

ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡

23

وَلَقَدْ رَآهُ بِالْأُفُقِ الْمُبِينِ

በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡

24

وَمَا هُوَ عَلَى الْغَيْبِ بِضَنِينٍ

እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡

25

وَمَا هُوَ بِقَوْلِ شَيْطَانٍ رَّجِيمٍ

እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡

26

فَأَيْنَ تَذْهَبُونَ

ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?

27

إِنْ هُوَ إِلَّا ذِكْرٌ لِّلْعَالَمِينَ

እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

28

لِمَن شَاءَ مِنكُمْ أَن يَسْتَقِيمَ

ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡

29

وَمَا تَشَاءُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ

የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡